እንኳን ደህና መጡ

Thumbnail Caption

በዚህ አዋጅ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች ልዩ እገዛ ለመስጠት የክልል ጉዳይ ዘርፍና የከተማ ልማት ዘርፍ ኃላፊነት ነበረው፡፡  ከዚያም 1998 . በአዋጅ ቁጥር 471/98 የአስፈፃሚ አካላትን ለማሻሻል በወጣው የማቋቋሚያ አዋጅ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አንዱ ነበር፡፡ በዚህ አዋጅ የከተማ ልማት ዘርፍን የማይመለከት ሲሆን በምትኩ አግባብነት ያላቸው ሕጐች እንደተጠበቁ ሆነው፤ በክልሎች ጥያቄ ሲቀርብ በክልሎች ውስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችና ግጭቶች በዘላቂነት የሚፈቱበትን ፖለቲካዊ መፍትሄ በማቅረብ፣ ተግባራዊ እንዲያደርግ እና በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች መካከል በመግባባትና በአጋርነት ላይ የተመሠረተ መልካም ግንኙነትና ትብብር እንዲኖር በማድረግ የፌዴራል ሥርዓቱ እንዲጠናከር የግንኙነቱ ማዕከል እንዲሆን ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ እንደዚሁም 2001 . በአዋጅ ቁጥር 641/2001 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለያዩ የኃይማኖት ተከታዮች መካከል እርስ በእርስ መከባበር፣ መቻቻልና መተማመን፣ ሠላምና ፀጥታ እንዲሰፍን ለማድረግ ግጭትን ለመከላከል እንዲቻል አግባብ ካላቸው ከማንኛውም አካላት ጋር ተባብሮ እንዲሰራ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ ከዚያም በአዋጅ ቁጥር 690/2002የአስፈፃሚ አካላት አደረጃጀትን ለማሻሻልና የልማትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ከላይ በተዘረዘሩት ተግባርና ኃላፊነት የሀይማኖት ተቋማት ምዝገባና ፈቃድ ተጨማሪ ተግባራት፣ የበጐ አድራጐት ድርጅቶችና የማህበራት ምዝገባ ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወን የማድረግ ሥልጣን ተስጥቶታል፡፡ የጦር መሣሪያ፣ የተኩስ ወይም ፈንጂ ለመያዝ ወይም ለመጠቀም ፈቃድ የመስጠትና የሽያጭ ሁኔታን  ለመወሰን ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

ሚኒስቴር /ቤቱ ልዩ ድጋፍ በሚሹ ክልሎች ፈጣንና  ተመጣጣኝ ልማት  ለማምጣት ሁለንተናዊ ድጋፍ ይሰጣል፡፡ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች የተለያዩ የፌዴራል ተቋማት የሚገኙበት ልዩ እገዛ ቦርድን የማስተባበር ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ በሀገሪቱ ሠላምና ፀጥታ ለማስፈን፣ ግጭቶችን መፍታትና መከላከል፣ እንደዚሁም በክልሎች መካከከል በመግባባትና በአጋርነት ላይ የተመሠረተ መልካም ግንኙነት ለማስፈን የፌዴራሊዝም ሥርዓቱ እንዲጠናከርና ፌዴራሊዝም ሥርዓት እንዲጐለብት ለማድረግ በመሠረታዊ አሠራር ለውጥ ጥናት መሠረት /ቤቱ 2002 . ጀምሮ ድርጅታዊ አወቃቀሩን በአዲስ መልክ ቀርጿል፡፡

 

አርእስተ ዜና

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባዔ ዓመታዊ ሪፖርቱን አቀረበ

ሴት ልጅ ግርዛትን በማውገዝ የሃይማኖት አባቶች መግለጫ ሰጡ

img

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የሰላምና የምክክር የጋራ ጉባኤ አንዳንድ ኃላፊነቶችን በመጨመር የስም ለውጥ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ጥር 28/2004ዓ.ም በግዮን ሆቴል ባካሄደው ስብሰባ ላይ እንዳስታወቀው ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ፈቃዱን በመውሰድ በሃይማኖችና እምነቶች መካከከል የቆየውን መልካም ግንኙነት ማጠናከርና በሃይማኖቶች ሽፋን የሚካሄዱ ሃይማኖታዊ ያልሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ በሃይማኖት አባቶች መካከል የጋራ መግባባት በመፍጠር አፍራሽ እንቅስቃሴዎችን መከላከል በዋናነት የሚሰራቸው ስራዎች መሆናቸውን አስታውቋል፡፡ መቻቻልና የጋራ መግባባትን ከመፍጠር በተጨማሪም በእናቶች ጤና፣ በስነ ተዋልዶና ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች ላይም ትኩረቱን አድርጎ እንደሚሰራ የጋራ ጉባኤው ዋና ፀሐፊ መጋቢ ዘሪሁን ደጉ ተናግረዋል፡፡




ጾታዊ ጥቃትን በማስቆም የህዳሴውን የልማት ጉዞ እናፋጥን!!

የዓለም የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቀንና የዓለም የነጭ ሪቫን ቀን በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሠራተኞች በደማቅ ሁኔታ ተከበረ፡፡

 

ህዳር 26 ቀን 2004 ዓ.ም የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም፣ ክቡር ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው፣ የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮችና ሁሉም ሠራተኞች በተገኙበት በመስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡




የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአል በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በድምቀት ተከበረ

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ህዳር 25/2004 ዓ.ም "ህገ መንግስታችን ለብዙህነታችን፣ ለአንድነታችንና ለህዳሴያችን" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል፡፡

በበዓሉ ወቅት  አቶ ጫኔ ገበየሁ እና አቶ ጸጋብርሃን ታደሰ ባቀረቧቸው ሁለት ሰነዶች ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ በመጀመሪያ አቶ ጫኔ ገበየሁ  "በኢ.ፌ.ዲ.ሪ  ህገ-መንግሥት የሲቪል ሰርቪስ  ተቋማት ሚናና የዜጎች ተጠቃሚነት"በሚል ርዕስ ላይ ሲያወያዩ በሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ማረጋገጥ፣ ማሳደግና ማጎልበት ዜጎች በሀገራቸው ፖቲካዊ፣ ማኅበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት የሚኖራቸውን ተጠቃሚነት ማሳየትና በመልካም አስተዳደር ግንባታው ባቤትነታቸውን ማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል፡፡


ስልጠናው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለመደገፍ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገለጸ
በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አዲሶችንም ጨምሮ በአራት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማለትም ህብረ-ብሔራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓት በኢትዮጵያ፣ ልማት ዴሞክራሲና የሃይማኖት አክራሪነት፣ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋገጥ የምንከተለው የትግል ስልትና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የምግብ፣ የአለባበስና የአምልኮ ስርዓት ለመደንገግ የወጣ መመርያ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከመስከረም 2004 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 2004 ዓ.ም ስልጠና ተሰጥቷል::


 
 
 

Web


News


Images